የቀዩ መኪና አሽከርካሪ በውስጥና በውጪ መስታወቶች ሲመለከት፣ በጥቁር የተመለከቱት አካባቢዎች ከዕይታው ውጪ ናቸው። በመሆኑም ሁለቱ ሰማያዊ መኪናዎች በፍጹም አይታዩትም።
በተመሳሳይ፣ ለአንድ የከባድ መኪና አሽከርካሪ በዙሪያው ሰፋ ያሉ ከዕይታ ውጪ የሆኑ አካባቢዎች አሉ። ይህንን በመገንዘብ ሌሎች አሽከርካሪዎች ከነዚህ ከማይታዩ ቦታዎች መራቅ አለብን። የከባድ መኪናው አሽከርካሪ እንደሚያየን ወይም እንደማያየን ለማወቅ፣ የከባድ መኪናውን አሽከርካሪ በውጪ መስታወቶቹ ለመመልከት እንሞክር። ካየነው እሱም መልሶ ሊያየን ይችላል ማለት ነው፤ ልናየው ካልቻልን ግን እሱም ሊያየን አይችልም እና ቶሎ መራቅ አለብን።